ኩዚ ማለትም “ዋትሌድ ስታርሊንግ” በስዋሂሊ ቋንቋ፣ አንበጣ የምትበላ ወፍ ስትሆን፣ ሰው ሰራሽ ምጥቀትን በመጠቀም መራቢያቸውን፣ መገኛቸውን እናም የበርሃ አንበጣዎችን የፍልሰት መንገዶች በአፍሪካ ቀንድ እናም በምስራቅ አፍሪካ ባሉ ሃገራት የሳተላይት መርጃን፣ የአፈር መመርመሪያ መረጃን፣ የምድር አየር-ትንበያ ምልከታን እና የማሽን ትምህርትን በመጠቀም ጸባያቸውን የሚያጠና መገልገያ ነው። ኩዚ የአፈር እርጥበትን፣ ንፋስን፣ የአይር እርጥበትን፣ የመሬት ሙቀትን የአትክልት ጠቋሚን፣ የአፈር መጠቆሚያ መረጃን በሳተላይት መረጃ የሰለጠነ የማሽን ትምህርት ሞዴልን ይጠቀማል።
እነዚህ ሁኔታዎች የአንበጣ መራቢያዎችን፣ የመንጋ አሰባሰብን እና አካሄዶችን ይለውጣል። ኩዚ ከፍተኛ ስጋት የሚባሉ ቦታዎችን በመለየት የአንበጣዎችን መራቢያ፣ መንጋ መሰብሰቢያ፣ እናም የፍልሰት ጥቃቶችን በማየት ገበሬዎች እና አርብቶ አደሮች የቅድሚያ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ይረዳል። ገበሬዎች እና አርብቶ አደሮች ኩዚን በመጠቀም የአንበሳ ጥቃትን እጅግ አስቀድሞ (የስልክ መልእክት ማግኘትን ጭምሮ) በማወቅ ጥቃት ሊደርስባቸው የሚችሉ ቦታዎችን እና እርሻዎችን በመለይት ማሳቸውንና ከብቶቻቸውን የመከላከል ስራ እንዲሰሩ ያግዛል።
በአሁን ላይ በአፍሪካ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ፣ ኬንያ እና ኡጋንዳ ያለ ነባራዊ የአንበጦች ሁኔታ።
ለአንበጣ መንጋ እንቅስቃሴ የሚሆኑ ሁሉም አማራጭ አቅጣጫዎች
በሳተላይት መረጃ፣ በመሬት የአየር ትንበያ ምልከታ መረጃ እና በማሽን ትምህርት ላይ የተመሰረተ የአንበጣዎች መራቢያ ጠቋሚ
ገበሬዎች ያሉበት አካባቢ የአንበጣ መንጋ ጥቃት ሊደርስበት ሲል የነጻ የመልእክት ማስታወቂያ ይደርሳቸዋል።
በበረሀ አንበጣ አመራር ውስጥ ቀድሞ ማወቅ እና መቆጣጠር በጣም ወሳኝ ተግባር ነው። ኩዚ የጥልቅ ትምህርትን በመጠቀም የአንበጣ መንጋ መሰብሰብ ሲጅምር ቀድሞ በመለየት ተገቢው እርምጃ አስቀድሞ እንዲወሰድ ማድረግ ያስችላል። እነዚህ እርምጃዎች በማህበረሰብ ደረጃ የመራቢያ ቦታዎችን መለየት የያዘ ሲሆን ይህም በአለም ላይ ያለን የምግብ እጥረት እና ረሃብን ለመከላከል እጅግ አስፈላጊ ነው።
በኩዚ ምክኒያት ቀጣዩ የአንበጣ ወረርሺኝ የማጋጠም እድሉ እጅግ በጣም ትንሽ ነው።
የሰለጠነ የማሽን ትምህርት ሞዴልን በመጠቀም የአፈር እርጥበትን፣ ንፋስን፣ የአይር እርጥበትን፣ የመሬት ሙቀትን የአትክልት ጠቋሚን፣ የአፈር መጠቆሚያ መረጃን በሳተላይት መረጃ ይሰጣል። እነዚህ ሁኔታዎች የአንበጣ መራቢያዎችን፣ የመንጋ አሰባሰብን እና አካሄዶችን ይለውጣል። ኩዚ ከፍተኛ ስጋት የሚባሉ ቦታዎችን በመለየት የአንበጣዎችን መራቢያ፣ መንጋ መሰብሰቢያ፣ እናም የፍልሰት ጥቃቶችን በማየት ገበሬዎች እና አርብቶ አደሮች የቅድሚያ ፣ ክ 2 - 3 ወር አስቀድሞ፣ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ይረዳል።
ገበሬዎች እና አርብቶ አደሮች ኩዚን በመጠቀም የአንበሳ ጥቃትን እጅግ አስቀድሞ (የስልክ መልእክት ማግኘትን ጭምሮ) በማወቅ ጥቃት ሊደርስባቸው የሚችሉ ቦታዎችን እና እርሻዎችን በመለይት ማሳቸውንና ከብቶቻቸውን የመከላከል ስራ እንዲሰሩ ያግዛል።
የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ፣ ትንበያ እና የመከላከል እና የመቆጣጠር ስትራቴጂን በመጠቀም እርምጃ በተገቢው ሰአት እና በብቁ ሁኔታ እንዲካሄድ መሰረት ይጥላል።